
፧
ትዳር
ትዳርን ስኬታማ ለማድረግ የሚረዳው ቁልፍ ስለ ጋብቻ በሚናገረው በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ተጠቅሷል
በትዳሩ ጋብቻ ውስጥ የነበረ ሰው ሁሉ ደስተኛ ትዳር ለመመሥረት ዋነኛው መንስኤ የአድናቂነትና የወዳጅነት መሠረተ ትምህርት እንደሆነ ያረጋግጥሉ. ትዳር ዘላቂ የሆነ የፍቅር መግለጫ ነው. በመተማመን ሁሉንም እድሎች ማሸነፍ ይችላሉ. ትዳራችሁን በጠንካራ ግንኙነታችሁ ላይ እምነት ይኑራችሁ. ለተሳካ ትዳር ተጨማሪ ሚስጥሮችን ለማግኘት, ስለ ጋብቻ የተሰጡትን ጽሑፎችን ያንብቡ.
የአለማችን ታላላቅ የሚባሉ ሰዎች በትዳር ላይ የሰጡት ጥቅሶች
ሆሜር
“ዓይናቸውን በዓይን የሚመለከቱ ሁለት ሰዎች እንደ ባልና ሚስት ቤት ሆነው እንዲቆዩ, ጠላቶቻቸውን የሚጋፉና ጓደኞቻቸውን የሚያስደስቱ ከመሆናቸው የበለጠ ዋጋ ያለው ወይም የበለጠ የሚደነቅ የለም.”
ሮበርት ሲዶድስ
“በጋብቻ ውስጥ ያለው ግብ እንደዚያ ማሰብ ሳይሆን በአንድ ነገር ማሰብ ነው.”
ሊንደን ቢ. ጆንሰን
“አንድ ሰው ሚስትን በደስታ ለማኖር ሁለት ነገሮች ያስፈልጋሉ, አንደኛው የራሷን መንገድ ለመያዝ የራሷን መንገድ, ሌላኛው እንዲኖራት ነው.”
ፐርል ኤስ ባክ
“ጥሩ ጋብቻ በግለሰቦችም ሆነ ፍቅራቸውን በሚገልጹበት መንገድ የሚፈቅድ ግለሰብ ነው.”
ሬኔር ማሪያ ሪልኬ
“ጥሩ ጋብቻ እያንዳንዱ ሰው የሌሎቹን ፀሐፊውን የሚሾምበት ነው.”
Simone Signoret
“ሰንሰለቶች በጋብቻ አላቆሙም, አመታትን, በመቶዎች የሚቆጠሩ ጥቃቅን ክሮች በጋራ አመሰግናለሁ.” ትዳራችሁን ለፍላጎት ሌላው ቀርቶ ከወሲብ ጋር የተቆራኘ ነው! “
ሶቅራጥስ
“እኔ ለናንተ ጥሩ ምክር ነው የምለው ማግባት ነው. ጥሩ ሚስት ካገኛችሁ, ደስተኛ ትሆናላችሁ, ካልሆነ ግን ፈላስፋ ትሆናላችሁ.”
ማርቲን ሉተር
“ከትዳር ትውፊት ይልቅ, የሚያምር, ወዳጃዊ እና የሚያምር ግንኙነት, ኅብረት ወይም ኩባንያ የለም”
አዲስ አድማስ በአንድ ወቅት ስለ ትዳር ያስነበበን
ያ የሚመጣው ሰው ባዶውን ሳይሆን የእራሱ የሆነ እውቀት፣ ልምድ፣ ሀብት ወይም በትንሹ የእራሱን ሀሳብ ይዞ ነው የሚመጣው፡፡
አንድ አእምሮ ከሚሰራ ሁለት አእምሮ በጋራ ቢሰራ የሚደመር እንጂ የሚቀነስ ነገር የለውም፡፡
ትዳር ማለት ችግርን ወይም ተግዳሮትን ለሁለት የሚያካፍል፣ ደስታ እና ስኬትን ደግሞ በሁለት የሚያበዛ ወዳጅ ማግኘት ማለት ነው፡፡
በሰው ልጅ እድገት ውስጥ ህፃንነት፣ ልጅነት፣ ወጣትነት፣ ጉልምስና እና እርጅና የማይቀሩ የህይወት ኡደቶች ናቸው፡፡ ታድያ በእነዚህ የእድሜ ደረጃዎች አንድ ሰው ሊያደርጋቸው የሚገቡ ወይም አይቀሬ የህይወት ክንውኖች አሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል ትዳር ወይም ጋብቻ አንዱ ነው፡፡
“…ጉርምስና ከመጣ በኋላ ወንዶች ለሴቶች እንዲሁ ሴቶችም ለወንዶች የሚኖራቸው አመለካከት ቀድሞ ከነበረው የተለየ ይሆናል ወይም በአጭሩ እርስ በእርስ የመፈላለግ ስሜት ይኖራቸዋል፡፡ ይህ ወንድን ወይም ሴትን የመፈለግ ተፈጥሯዊ ስሜት በግዜ ሂደት አድጎ ጋብቻ የምንለው ደረጃ ላይ ይደርሳል፡፡ ስለዚህ ጋብቻ የምንለው አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ግንኙነት የሚመሰርቱበት እና ቀጣይ ኑሯቸውን አብረው የሚኖሩበት ጥምረት ወይም አንድነት ነው ማለት እንችላለን፡፡ ወይም በአጭር ቃል ጋብቻ ወይም ከዛ የሚቀድመው የተቃራኒ ፆታ ግንኙነት ተፈጥሯዊ ለሆነ ስሜት ምላሽ መስጠት ነው ብለን ልንተረጉመው እንችላለን፡፡…”
ይህን ያሉን የስነልቦና ባለሙያ የሆኑት አቶ ከበደ በከሪ ሲሆኑ አቶ ከበደ በጋብቻ ዙሪያ በርካታ መፃህፍትን የፃፉ ሲሆን የምክር አገልግሎት በመስጠት የእረዥም አመታት ልምድ አካብተዋል፡፡ ምንም እንኳን በጋብቻ መልካምነት ላይ ብዙዎች ቢስማሙም ጥቂት የማይባሉ ሰዎች በግል ህይወታቸው ከተለማመዱት፣ በአካባቢያቸው ካዩት እና ከሰሙት ነገሮች በመነሳት ስለ ጋብቻ አሉታዊ የሆነ አስተሳሰብን ሊያራምዱ ይችላሉ የሚሉት ባለሙያው የሰዎች ድርጊት በአብዛኛው የሚወሰነው በአእምሮአቸው ውስጥ ባለው አስተሳሰብ በመሆኑ ሰዎች የጋብቻን መልካምነት እንዳይረዱ ብሎም የተሳሳተ አመለካከት እንዲኖራቸው ምክንያት የሚሆኑ አስተሳሰቦች ወይም ልምምዶች በርካታ እንደሆኑም ጨምረው ይጠቅሳሉ፡፡
“…ሁሉም ሰው ጋብቻን አይፈራም፡፡ ነገር ግን ጋብቻን የማይፈልጉ እና ሀላፊነት ወዳለበት ህብረት ለመግባት የሚፈሩ ሰዎች ይኖራሉ፡፡ እንግዲህ ይህ ፍርሀት ወይም አሉታዊ የሆነ አመለካከት የእራሱ የሆነ መነሻ ምክንያት ይኖረዋል፡፡ የሁሉም ምክንያት ግን ተመሳሳይ ላይሆን ይችላል፡፡…”
እነዚህ ምክንያቶች እጅግ በርካታ እና የተለያዩ ቢሆኑም የቤተሰብ የኋላ ታሪክ አንዱ እና ግንባር ቀደም ከሚባሉት ውስጥ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ ሰዎች በቤተሰቦቻቸው የትዳር ህይወት ውስጥ ከሚያዩት ነገር በመነሳት ስለጋብቻ መልካም ወይም መጥፎ አመለካከት ሊኖራቸው እንደሚችል አቶ ከበደ ይናገራሉ፡-
“እኛ ባደግንበት ቤተሰብ ውስጥ አባት እና እናታችን ጥሩ የሆነ የባልና ሚስት ግንኙነት ከሌላቸው ወይም ስለ ጋብቻ ስናስብ አርአያ ሊሆን የሚችል ቤተሰብ ከሌለን የእነሱን ችግር እና መጥፎ ግንኑነት በማየት ወደ እንደዛ አይነት ህይወት ላለመግባት በሚል እንሸሻለን፡፡ ነገር ግን በተቃራኒው ጥሩ የትዳር ግንኙነት ያላቸው እና ምሳሌ መሆን የሚችሉ ቤተሰቦች ካሉን እኔም መቼ አግብቼ እንደእነሱ አይነት ህይወት ይኖረኛል? የሚል ጉጉት ሊያድርብን ይችላል፡፡ ስለዚህ የቤተሰባችን የትዳር ሁኔታ እዚህ ላይ የሚኖረው ሚና ይህ ነው የሚባል አይደለም፡፡..”
የሰላም ታሪክ ለዚህ አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡ ሰላም በሀያዎቹ መጀመሪያ ላይ የምትገኝ ወጣት ስትሆን ከአንድ አመት በፊት የነበረውን የትዳሯን አጀማመር እንዲህ ታስታውሰዋለች፡-
“…ከማግባቴ በፊት ትዳር በጣም የሚያስፈራ ነገር ይመስለኝ ነበር ባጠቃላይ ስለ ትዳር ያለኝ አመለካከት ጥሩ አልነበረም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ቤተሰቦቼ ጥሩ የትዳር ህይወት ስላልነበራቸው ይመስለኛል፡፡ በዚህም ምክንያት ከጓደኛዬ ጋር ሶስት አመት ያህል አብረን ከቆየን በኋላ የትዳር ጥያቄ ሲያቀርብልኝ በጣም ነበር የደነገጥኩት፡፡ እሺታዬንም ቶሎ አልነገርኩትም፡፡ ከብዙ ማንገራገር በኋላም ለማግባት ስወስን የቤተሰቦቼን ተቀባይነት ስላገኘሁ እሱም ሌላ ችግር ነበር፡፡”
ሌላዋ ያነጋገርናት ወጣት ሜሮን ትባላለች ሜሮንም ይህን የሰላም ሀሳብ ብትጋራም ይህ ጫና ወይም ጣልቃ ገብነት የወላጅ ወይም ያሳዳጊ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ከማህበረሰሁ የሚመነጭ ነው ትላለች፡-
“…ይህ አይነቱ ጫና ከቤተሰብ ብቻ የሚመጣ አይመስለኝም፡፡ እንደውም ብዙ ግዜ ከቤተሰብሽ ይልቅ ማግባትሽን ተቃውመው አሉታዊ የሆነ አስተያየት የሚሰጡሽ በአካባቢሽ ያሉ ሰዎች ናቸው፡፡ ሳታገቢ ከዘገየሽም እንደዛው። ለዚህ ምክንያነቱ ምን እንደሆነ በትክክል ለማወቅ ያስቸግራል። ግን አንዳንዱ ገና ልጅ ናት ብሎ ስለሚያስብ ሊሆን ይችላል ወይም ከምታገቢው ሰው ማንነት በመነሳት ሊሆን ይችላል ወይም ሌሎች ምክንይቶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ያምሆነ ይህ ግን ተፅእኖ ማድረጋቸው አይቀርም፡፡…”
ቤተሰብ፣ አሳዳጊ እንዲሁም በትልቁ ማህበረሰብ በዚህ እረገድ የሚኖረውን ጫና ወይም ተፅእኖ መካድ ባይቻልም ለዚህ ትልቁን ሀላፊነት መውሰድ ያለባቸው ግለሰቦች እራሳቸው መሆን ይኖርባቸዋል የሚለው ወጣት ሄኖክ ነው፡፡
“…እዚህ ላይ ቤተሰብ ተፅእኖ አያደርግም ማለት አይቻልም ነገርግን እንደ እኔ አመለካከት ወንድ ልጅ ስለ ሴት ወይም በተቃራኒው ሴት ልጅ ስለ ወንድ የሚኖራቸው አመለካከት በእራሱ ሰዎች በጋብቻ አብረው እንዳይኖሩ ወይም ጋብቻን እንዲፈሩ ከሚያደርጉ ምክንያቶች ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚይዝ ይመስለኛል፡፡ ሌላው ትልቁ ባጠቃላይ ስለትዳር የሚኖረን አመለካከት በእራሱ ተፅእኖ ያለው ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ሰው የሚያስበውን ነው የሚሆነው፡፡…”
እርግጥ ቤተሰብ ወይም አሳዳጊ በዚህ ላይ ተፅእኖ ያደርጋል? ባለሙያው ለዚህ ጥያቄ የሰጡን ምላሽ እንዲህ የሚል ነበር፡-
“…አንዳንድ ግዜ ልጆች ለማግባት በሚወስኑበት ግዜ ቤተሰብ ይህንን ተቃውሞ ጫና ሊፈጥር ይችላል፡፡ ሁሉም ባይሆንም አንዳንዶች ከልጆቻቸው የሚያገኙት ጥቅም ወይም ድጋፍ ይኖርና ልጆቻችን ካገቡ ይህ ጥቅም ሊቀርብን ይችላል ወይም ሊረሱን ይችላሉ ከሚል ስጋት ጋብቻውን ሊቃወሙ ይችላሉ፡፡ እርግጥነው ወላጅ ለልጁ መልካም የሆነውን ነገር ያስባል እንዲሆንም ይፈልጋል ነገርግን አንዳንዴ እንዲህ አይነት ሁኔታ ሊያጋጥም ይችላል፡፡ ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ እድሜህ/ሽ ገና ነው ወይም ይህ/ች ሰው አይሆንሽም/አትሆንህም በሚሉ ምክንያቶች ወላጆች ልጆቻቸው ወደ ትዳር እንዳይገቡ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ …በዚህ ላይ ወላጆች ምንም አይነት ጣልቃ ገብነት ሊኖራቸው አይገባም ማለት ባይቻልም በዚህ ላይ ትልቁ የመወሰን ሀላፊነት የተጋቢዎቹ መሆን ኖርበታል፡፡…”
የኢኮኖሚ አቅም ሰዎች ጋብቻን እንዲፈሩ ወይም ብቸኝነትን እንዲመርጡ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል በዋነኛነት የሚጠቀስ ነው፡፡ ምንም እንኳን በኢኮኖሚ እራስን መቻል እና መሰረታዊ የሰው ልጅ ፍላጎቶችን ማሟላት ትዳር ከመመስረቱ በፊት ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ቢሆንም ትዳር በገንዘብ ወይም በቁሳቁስ ላይ መመስረት የለበትም ይላሉ ባለሙያው፡-
“…በቂ የሆነ ገንዘብ የለንም፡፡ ስለዚህ ብቻዬን ብቸገር ይሻላል… የሚሉ አስተያየቶች ብዙ ግዜ ይደመጣሉ፡፡ እንግዲህ ምንያህል ነው ሰውን ሊያኖር የሚችለው? የሚለው አንፃራዊ ነው፡፡ እንደ እይታችን፣ እንደምንኖርበት ማህበረሰብ እና አካባቢ ይለያያል፡፡ ነገርግን መሰረታዊው ጥያቄ እንደ አንድ ሰው ለብቻ መኖር ከቻልን ሌላው ሰው ሲመጣ ለምን ሀሳብ ይሆንብናል? ምክንያቱም ያ የሚመጣው ሰው ባዶውን ሳይሆን የእራሱ የሆነ እውቀት፣ ልምድ፣ ሀብት ወይም በትንሹ የእራሱን ሀሳብ ይዞ ነው የሚመጣው፡፡ ስለዚህ አንድ አእምሮ ከሚሰራ ሁለት አእምሮ በጋራ ቢሰራ የሚደመር እንጂ የሚቀነስ ነገር የለውም ስለዚህ ከአንድ ሁለት ይሻላል።…”
ሌላው የትዳርን አሉታዊ ጎን ከሚሰብኩ ሰዎች የሚያነሱት ምክንያት “ትዳር ነፃነትን ያሳጣል” የሚል ነው፡፡ እውን ትዳር ነፃነትን ያሳጣል? ለሰላም ያነሳንላት ጥያቄ ነበር፡፡
“በዚህ አሳብ በፍፁም አልስማማም ምክንያቱም ትዳር ከያዝኩበት ቀን አንስቶ እስከአሁን ድረስ ነፃነቴን የሚያሳጣ ወይም በጓደኝነት ግዜ ከነበረን ምንም የተለየ ነገር አላየሁም።” እኔእና ባለቤቴ ከመጋባታችን በፊት በጣም ጥሩ የሚባል የፍቅር ግዜ አሳልፈን በሚገባ ተዋውቀናል፡፡ ስለዚህ እንደ እኔ አመለካከት በመጋባታችን ብቻ ምንም የሚፈጠር አዲስ ነገር አይኖርም፡፡ ምንአልባት ይህ አይነቱ ችግር ሊፈጠር የሚችለው በሚገባ ሳትተዋወቂ ወይም ሳትናበቢ ወደ ትዳር የምትሄጂ ከሆነ ብቻ ነው፡፡”
ይህ አይነቱ አመለካከት ከእራስ ወዳድነት የሚመነጭ ነው፡፡ ያለን ደግሞ ሌላው ለዚህ ፅሁፍ ግብአት ይሆነን ዘንድ ሀሳባቸውን ከሰጡን ወጣቶች መካከል ባለትዳር እና የአንድ ልጅ አባት የሆነው ዳንኤል ነው፡፡
“…እኔ ይህንን እንደ እራስ ወደዳድነት ነው የማየው፡፡ በእርግጥ ነፃነቱን የሚጠላ ማንም የለም ነገርግን ትዳር ለእኔ እስር ቤት ማለት አይደለም፡፡ ትዳር ለእኔ ለሌላው በመኖር ልዩ ደስታ የሚገኝበት ህይወት ነው፡፡ በእርግጥ ትዳር ለሌላው በቂ ግዜ መስጠትን ይጠይቃል ምናልባት ሰዎች እንደ ነፃነት ማጣት የሚቆጥሩት ይህንን ሊሆን ይችላል፡፡ ነገርግን እኔን ይበልጥ የሚያዝናናኝ ከባለቤቴ እና ከልጄ ጋር የማሳልፈው ግዜ ነው፡፡…”
የግለሰቦች ምርጫ እንደተጠበቀ ሆኖ ማግባት ካለ ማግባት የበለጠ ጥቅም አለው የሚሉት ባለሙያው አንድ ሰው እድሜው ለትዳር ከደረሰ በኋላ ትዳር መስርቶ ለመኖር ቢወስን እና ቢያገባ ካላገቡ ሰዎች የበለጠ ስኬታማ ህይወት እንደሚኖረውም ይናገራሉ፡፡
“…ትዳሩ በጣም ታስቦበት የተመሰረተ ተጋቢዎቹም በስብእበና፣ በህይወት ግባቸው፣ በህይወት ዘይቤአቸው እንዲሁም በእሴቶቻቸው የሚጣጣሙ ከሆነ ማግባት ካለማግባት በእጅጉ የተሻለ ነው፡፡ …በአለማችን ላይ ያሉ ስኬታማ የሚባሉ ሰዎች ብዙዎቹ ትዳር ያላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ አልፎ አልፎ ያላገቡ ሰዎችም ሊኖሩ ይችላሉ። ነገርግን ጠቅለል አድርግን እንደ ማህበረሰብ ስንመለከት በህይወት ፍሬያማ ለመሆን በጣም የቅርብ የሆነ፣ የእኔ የምንለው ሰው ያስፈልገናል፡፡ …ስለዚህ ትዳር ማለት ችግርን ወይም ተግዳሮትን ለሁለት የሚያካፍል፣ ደስታ እና ስኬታችንን ደግሞ በሁለት የሚያበዛ ወዳጅ ማግኘት ማለት ነው፡፡
ቂምን መተው የሚቻልበት መንገድ
ተፈታታኙ ነገር
የትዳር ጓደኛሽ * የተናገረውን ወይም ያደረገውን መጥፎ ነገር መርሳት አልቻልሽም፤ የተናገራቸው ሸካራ ቃላትና የፈጸመው አሳቢነት የጎደለው ድርጊት ከአእምሮሽ ሊፋቁ አልቻሉም። በዚህም የተነሳ በአንድ ወቅት የነበረሽ ፍቅር በቂም ተተክቷል። ፍቅር አልባ የሆነውን ትዳርሽን ችለሽ ከመኖር ሌላ አማራጭ እንደሌለሽ ይሰማሻል። በዚህም ጭምር በትዳር ጓደኛሽ ላይ ቂም ይዘሻል።
ቂምና ጉዳቱ በጥቂቱ
ማወቅ የሚኖርብሽ ነገር
ቂም መያዝ ከባድ ሸክም ስለሚሆንባችሁ ትዳራችሁን መምራት እንዲከብዳችሁ ያደርጋል
ቂም ትዳርን ሊያፈርስ ይችላል። ለምን? ምክንያቱም ፍቅርን፣ ሐቀኝነትንና ታማኝነትን ጨምሮ ለትዳር መሠረት የሆኑት ባሕርያት እየከሰሙ እንዲሄዱ ያደርጋል። ከዚህ አንጻር ቂም በትዳር ውስጥ በተፈጠረ ችግር ሳቢያ የሚመጣ ነገር ሳይሆን ራሱ በትዳር ውስጥ የሚፈጠር ችግር ነው።
ቂም የምትይዢ ከሆነ የምትጎጂው ራስሽን ነው። ቂም መያዝ ራስን በጥፊ እየመቱ ሕመሙን ሌላ ሰው እንዲሰማው ከመጠበቅ ተለይቶ አይታይም። ማርክ ዚከል፣ ሂሊንግ ፍሮም ፋሚሊ ሪፍትስ በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል፦ “ቂም የያዛችሁበት የቤተሰብ አባል ስለ ጉዳዩ ምንም ስለማያውቅ በደስታ ሕይወቱን መምራቱን ቀጥሎ ይሆናል፤ ምናልባትም እናንተ የምታሳዩት ስሜት ምንም አልረበሸው ይሆናል።” ዋናው ነጥብ ምንድን ነው? ዚከል “ቂም የሚያደርስባችሁ ጉዳት ያስቀየማችሁ ሰው ካደረሰባችሁ ጉዳት ይበልጣል” ብለዋል።